ዓለምን እንዳላይ (ዝና ከበሬታ) Original Song by Dereje Kebede | Lighthouse Worship
Live worship session at Lighthouse cafe
አለምን እንዳላይ አይኔን ተቆጣጠር
ቀስ በቀስ እንዳልሄድ ወደ አታላይ ሃገር
አንተ ብቻ እንድትሆን ማርና ወተቴ
በእግርህ ስር እንድኖር ይሄ ነው ፀሎቴ
ዝናም ከበሬታም ይጠፋሉ ፈጥነው
አይደለም ነዋሪ ሃብትም እንደ ጢስ ነው
ዘለአለም ነዋሪ ኢየሱስ ብቻ ነው
ዘለአለም ዘላቂ ኢየሱስ ብቻ ነው
መንፈሳዊ አይኖቼን ክፈታቸውና
ልመልከት ጌታ ሆይ ደጉን እንደገና
የጥንቱን ፍቅሬን ዳግም ብታለብሰኝ
አያለሁ አጥርቼ ጉምም አይሸፍነኝ
አተርፍ ባይ አጉዳይ መሆን ያስፈራኛል
ከአንተ ጋር መሆኑ እጅግ ያዋጣኛል
ህይወት መች ይሰጣል ወርቅ ቢያብረቀርቅ
ቅብዝብዝ ይሆናል ሰው ከአንተ ቤት ሲርቅ
የሰጠኅኝን ግብ እንዳልጥለው ወዲያ
እንዳልገባ ሲኦል ከህይወት በስቲያ
ይቅርብኝ እንግዲህ ብናኙ ግሳንግስ
ልኑር በአንተ ጥላ ልቤን ለአንተ ላፍስስ
ኢየሱስ ዘላለም
ዘላቂ አንተ ብቻ አኮ ነህ
Live worship session at Lighthouse cafe
አለምን እንዳላይ አይኔን ተቆጣጠር
ቀስ በቀስ እንዳልሄድ ወደ አታላይ ሃገር
አንተ ብቻ እንድትሆን ማርና ወተቴ
በእግርህ ስር እንድኖር ይሄ ነው ፀሎቴ
ዝናም ከበሬታም ይጠፋሉ ፈጥነው
አይደለም ነዋሪ ሃብትም እንደ ጢስ ነው
ዘለአለም ነዋሪ ኢየሱስ ብቻ ነው
ዘለአለም ዘላቂ ኢየሱስ ብቻ ነው
መንፈሳዊ አይኖቼን ክፈታቸውና
ልመልከት ጌታ ሆይ ደጉን እንደገና
የጥንቱን ፍቅሬን ዳግም ብታለብሰኝ
አያለሁ አጥርቼ ጉምም አይሸፍነኝ
አተርፍ ባይ አጉዳይ መሆን ያስፈራኛል
ከአንተ ጋር መሆኑ እጅግ ያዋጣኛል
ህይወት መች ይሰጣል ወርቅ ቢያብረቀርቅ
ቅብዝብዝ ይሆናል ሰው ከአንተ ቤት ሲርቅ
የሰጠኅኝን ግብ እንዳልጥለው ወዲያ
እንዳልገባ ሲኦል ከህይወት በስቲያ
ይቅርብኝ እንግዲህ ብናኙ ግሳንግስ
ልኑር በአንተ ጥላ ልቤን ለአንተ ላፍስስ
ኢየሱስ ዘላለም
ዘላቂ አንተ ብቻ አኮ ነህ
